ለጥገኝነት ጠያቂዎችና ጥገኝነት ላገኙ በነጻ ስልክ የሚደውሉበት ቁጥር, 800 905 570, (እንዲሁም በላይካ ሞባይል ለሚደውሉ: +39 3511376335 ) በአርቺ ብሔራዊ ማሕበር የውጭ ዜጎችና የጥገኞች ጽ/ቤት የሚተዳደር ሆኖ፡ ስደተኞችን ሕግን በሚመለከተ፣ በትርጉምና ከህብረተሰቡ የሚወሃዱበት መንገድ ለመድረስ የሚያስችል፡ ከመደበኛና ከሞባይል ስልኮች በነጻ መደወል የሚያስችል የስልክ ኣገልግሎት መዘርጋት ፈለገ።
አገልግሎቱ የተጀመረው እ.ኤ.አ. በ 2006 በ “ኢኳል ኢንተግራርሲ” ፕሮጀክት የሙከራ እንቅስቃሴ ነበር: በ ANCI (የጣልያን ማዛጋጃ ቤቶች ማሕበር)ድጋፍና በሚኒስትሮች ምክር ቤት ፕሬዝዳንት በሚሰበሰበው የ 8 × 1000 የገንዘብ ድጋፍ ኣገልግሎቱን ቀጠለ ፡፡ እ.ኤ.አ. በ 2013/2014 ጽህፈት ቤቱ በቤተሰብ ውህደት አሰራሮች አያያዝ እና በዱብሊን II እና III ስምምነቶች የተሰጡትን አሰራሮች አያያዝ በተመለከተ የተባበሩት መንግስታት የስደተኞች “የትግበራ አጋር” ሆኖ እውቅና ተሰጠው ፡፡ በተጨማሪም ኡናር (UNAR) በ (እ.ኤ.አ. ሰኔ 2013 / ሰኔ 2015) ውል የፈረመ ሲሆን በዚህ በኩል አለም አቀፍ ጥበቃ አመልካቾችና ለአለም አቀፍ ጥበቃ ላገኙ፡ በየትኛው የአድልዎ ጥቃት ላይ ጽ / ቤቱን ከጀርባው ልዩ ባለ ሙያተኛ ጋር በመሆን ኣገልግሎት እንዲሰጥ አደራ ብሎታል ፡፡
አገልግሎቱ ለብዙ ጥገኝነት ጠያቂዎችና ስደተኞች የማጣቀሻ ስፍራ መሆኑ የተረጋገጠ ነው ፣ በተለይም ከተቋሙ በቂ ምላሽ ባለመገኘታቸው ፣ ከመቀበያ ፣ ከሕግ ምክርና ድጋፍ አገልግሎቶች በጭራሽ ተጠቃሚ ላልሆኑ። ግዜውን እየጨመረ በሄደ ቁጥር፡ የስልክ ጥሪዎችን በማለፍ ኑሜሮ ቬርደ፡ ኣንድ ፕላትፎርም በማዘጋጀት በጥገኝነት ሕግ መስክ ተሰማርተው በቋሚ ለውጦች ጋር በሚታገሉ ኦፕሬተሮች፣ ጠበቆችና የሕግ ባለሙያዎች መካከል የልምድ ልውውጥ መድረክም ሆኗል ፡፡
ኑሜሮ ቬርደ ለጥገኝነት ጠያቂዎችና ስደተኞች ከክፍያ ነፃ ስልክ ቁጥር ከሰኞ እስከ ዓርብ ከ 9.30 እስከ 17.30 መልስ ይሰጣል፡ እና በቀን ለ 24 ሰዓታት በብዙ ቋንቋዎች መልእክት የሚቀበል ማሽን ኣገልግሎት ላይ ኣውለዋል።
መይል: numeroverderifugiati@arci.it