እ.ኤ.አ. ጥር 26 ቀን 2023 የጠቅላይ ሚኒስትር የሚኒስትሮች ምክር ቤት ዲሴምበር 29 ቀን 2022 (የፍሰት ድንጋጌ) ታትሟል ፣ ይህም ለሥራ ወደ ጣሊያን የሚገቡ የውጭ አገር ሠራተኞችን ኮታ አስቀምጧል።
ከፍተኛው የመግቢያ ብዛት 82,705 ሰዎች ሲሆን ከእነዚህ ውስጥ፡–
- 44,000 ለወቅታዊ የሥራ ምክንያቶች;
- 38,705 ለወቅታዊ ባልሆኑ የሥራ ምክንያቶች፣ ከእነዚህም ውስጥ፡-
- 30.105 ወቅታዊ ያልሆኑ የበታች ሥራ ግቤቶች የተያዘ፤ በትራንስፕርት መጓጓዣ፣ በግንባታና በቱሪዝም፡ ሆቴል፣ መካኒክ፣ ቴሌኮሙኒኬሽን፣ ምግብ ማዘጋጀት፣ በመርከብ ግንባታ ዘርፎች ውስጥና የራስ ሥራ።
- 1,000 ለወንድና ሴት ሰራተኞች በውጭ ሀገር የሰለጠኑ በሚኒስቴሩ የፀደቁ መርሃ ግብሮች፣ ከመሄድ በፊት ፕሮጀክትን ጨምሮ ማመልከቻዎችን ይስባል።
የመኖሪያ ፈቃዶችን መለወጥ – ከታች ከተዘረዘሩት የመኖርያ ፈቃድ ያላቸው ሰዎች ፈቃዱን ለመለወጥ መጠየቅ ይችላሉ፦
- ወቅታዊ የሥራ መኖርያ ፈቃዶች
- ለትምህርት ዓላማዎች የመኖርያ ፈቃዶች
- በሌሎች የአውሮፓ ህብረት አገሮች ውስጥ ያልተገደበ የመኖሪያ ፈቃድ
እንዴት ማመልከት እንደሚቻል
ከቅርብ ዓመታት ወዲህ ከነበረው የኣሰራር ሁኔታ በተለየ፡ ለሠራተኛው እንዲቀጠር የፈቃድ ጥያቄን ከመላኩ በፊት፣ አሠሪው ሥራውን ለመሙላት በብሔራዊ ክልል ውስጥ ያሉ ሌሎች ሠራተኞች እንደሌሉ አሠሪው ብቃት ካለው የቅጥር ማእከል ጋር ማረጋገጥ ይኖርበታል።
ይህንን ማረጋገጫ ለመፈጸም አሠሪው ይህንን ቅጽ በመሙላት ለሠራተኞች ጥያቄ ወደ የቅጥር ማእከል መላክ አለበት። መመርያው እዚህ ኣንብብ guida per i datori/datrici di lavoro.
የፍቃድ ጥያቄው ሊደረግ የሚችለው፡–
ሀ) የቅጥር ማእከል ለቀረበው ጥያቄ ምላሽ ካልሰጠ፣ ጥያቄው ከቀረበበት ቀን ጀምሮ በአስራ አምስት የስራ ቀናት ውስጥ፤
ለ) በቅጥር ማእከል የተዘገበው ሠራተኛ ለቀጣሪው ለተሰጠው ሥራ ተስማሚ ካልሆነ
ሐ) ከቅጥር ማእከል የተላከው ሠራተኛ ለቃለ መጠይቁ አሳማኝ ምክንያት በሌለበት ሲቀር፡ ከጥያቄው ቀን ጀምሮ ቢያንስ ከ 20 የሥራ ቀናት በኋላ።
ከነዚህ ሁኔታዎች ውስጥ አንዱ ከተከሰተ አሠሪው ለሥራ ፈቃድ ማእከል፡ በራሱ ማረጋገጫ የተጻፈ ሰነድ ከማመልከቻው ጋር በማያያዝ ማስታወቅ አለበት።
በደንብ ያስተውሉ፡ በብሔራዊ ክልል ውስጥ ያሉ ሰራተኞች አለመኖራቸውን ማረጋገጥ፡ ለወቅታዊ ሰራተኞች እና በውጭ አገር የሰለጠኑ ሰራተኞች አስፈላጊ አይደለም።
ማመልከቻዎቹ ከቀረቡ ከ 30 ቀናት በኋላ ምንም እንቅፋቶች ከሌሉ ፈቀዳው በቀጥታ ይወጣና ኑላ ኦስታው ይላካል – በቀጥታ በመስመር ላይ ከተላከ ፡ በትውልድ ሀገሮች የኢጣሊያ ዲፕሎማሲያዊ ተወካዮች (ኤምባሲዎች) ማመልከቻው ከቀረበበት በ 20 ቀናት ውስጥ የመግቢያ ቪዛ መስጠት አለባቸው ።
