የመኖሪያ ፈቃዶችን ለመለወጥና የአውሮፓ ህብረት ላልሆኑ ዜጎች ወደ ውጭ አገር በማሰልጠን ፕሮጀክቶች ውስጥ ለመግባት ማመልከቻ የማቅረቢያ ቀነ፡ ገደብ እስከ መስከረም 30 ቀን 2022 ተራዝሟል። የፍሰት ድንጋጌው (የዲሴምበር 21 ቀን የሚኒስትሮች ምክር ቤት ፕሬዚዳንት ድንጋጌ) ወደ ጣሊያን ለመግባት የሚችሉትን የውጭ ሰራተኞች ከፍተኛውን ኮታ በ 69,700 አስቀምጧል።
በዚህ መሰረት፣ ማመልከቻዎች አሁንም ሊቀርቡ ይችላሉ:
1) ወደ የስራ መኖርያና ለግል ሥራ ፈጣሪነት የመኖሪያ ፈቃዶችን ለመለወጥ የጠየቁ
እስካሁን ካለው ኮታ ጋር ሲነጻጸር ወደ 45% የሚጠጉ ናቸው።
2) የአውሮፓ ህብረት ላልሆኑ ዜጎች ወደ ጣሊያን ለመግባት በትውልድ አገራቸው የስልጠናና የትምህርት መርሃ ግብሮችን ላጠናቀቁ
በእውነቱ፣ በትውልድ አገራቸው የትምህርትና የሥልጠና መርሃ ግብሮችን ላጠናቀቁ ሠራተኞች ቅበላ እስከ አሁን በቁጥር 100 አላለፈም (በሐምሌ 25 ቀን 1998 በወጣው የሕግ ድንጋጌ አንቀጽ 23 አንቀጽ 286 መሠረት)።
እንዴት ማመልከት እንደሚቻል
የአሰራር ሂደቱን ለመጀመር አሰሪው (ጣሊያን ወይም ጣሊያን ውስጥ በህጋዊ መንገድ የሚኖር የውጭ ሀገር ዜጋ) የአውሮፓ ህብረት ያልሆነ ሰራተኛ ለመቅጠር ፍቃድ መጠየቅ አለበት በዚህ ሊንክ ኦንላይን በመሙላት: https://nullaostalavoro.dlci.interno.it
ማመልከቻ ለማስገባት እስከ ሴፕቴምበር 30 – 2022 ግዜ ይኖራል(ማርች 17 – 2022 የሚለውን ተራዝመዋል) እና ቀድመው ላስገቡ በቅደም ተከተል ቅድሚያ ይሰጣል።
ማሳሰቢያ፡ አፕሊኬሽኑን ለመሙላት የSPID መታወቂያ መያዝ ያስፈልጋል
በሴፕቴምበር 30 – 2022 የሚያበቃው Before You Go ፕሮጀክት እስካሁን በጣሊያን ውስጥ የስደት መንገድ ለመምራት ያሰቡ 583 ሰዎችን ለማካተት አመቻችቷል: በትውልድ አገራቸው ከባህላዊ፣ ከቋንቋ፣ ከማህበራዊ እና ከስራ እይታ አንጻር ማዘጋጀ። በፕሮጀክቱ ላይ ተጨማሪ መረጃ ለማግኘት ይህንን ሊንክ ይጎብኙ።
4,223 Visite totali, 1 visite odierne